የኦሮሞ ማህበረሰብ ገለፃ ለአሜሪካን እንደራሴዎች
ረቡዕ፣ ሚያዝያ 12 2008ማስታወቂያ
በአሜሪካን ነዋሪ የሆኑ የኦሮሞ ማህበረሰብ አባላት ከጥቂት ወራት በፊት በኦሮምያ ክልል ስለተካሄደው ህዝባዊ አመፅና መንግሥት ስለወሰዳቸው እርምጃዎች ለአሜሪካን የህዝብ እንደራሴዎች ገለፃ አደረጉ ። እነዚሁ ከ30 የተለያዩ የአሜሪካን ክፍለ ግዛቶች የተሰባሰቡት የኦሮሞ ማህበረሰብ አባላትና የመብት ተሟጋቾች ማብራሪያውን የሰጡት ለየሚገኙባቸው ክፍለ ግዛቶች ና ዋሽንግተን ዲሲ ላሉ የህዝብ እንደራሴዎች ነው ። የማህበረሰቡ አባላት ዩናይትድ ስቴትስ ለኢትዮጵያ መንግሥት የምትሰጠው የልማትና የጦር መሣሪያ ድጋፍ በኦሮምያ ክልል የተከሰተውን ተቃውሞ በኃይል ለመቀልበስ ውሏል ሲሉ ይከሳሉ ። የዋሽንግተን ዲሲው ዘጋቢያችን ናትናኤል ወልዴ ዝርዝሩን አዘጋጅቷል ።
ናትናኤል ወልዴ
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሀመድ