የኦሮሞ ህዝብ ኮንግረስ አቤቱታ
ዓርብ፣ መጋቢት 9 2003ማስታወቂያ
ኢትዮጵያ ውስጥ፤ በኦሮሚያ መስተዳድር ፤ በተለያዩ ጊዜያት ፤ እስካሁን ከ 102 በላይ የሚሆኑ ቢሮዎቹ፤ በ ኢ ህ አ ዴግ መንግሥት እንደተዘጉበት የገለጠው የኦሮሞ ህዝብ ኮንግረስ ፣ ከዚህ ቀደም ያጋጥሙት ከነበሩት መሰናክሎች በተጨማሪ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ፤ቀድሞ የፓርላማ አባላት የነበሩና ታዋቂ አባላቱ ፣ ከየቦታው ፣ በፌደራል ፖሊስ እየተያዙ መታሠራቸው እየተነገረ ነው። «አሁን እየተወሰደ ያለው እርምጃ ፤ ድርጅታችንን ሙሉ በሙሉ ባገር ውስጥ ለመዝጋት የሚደረግ ጥረት ይመስላል» ያሉት የፓርቲው ዋና ጽ/ቤት ምክትል ኀላፊ አቶ ኦልባና ለሊሣ፤ የኢትዮጵያ ህዝብና ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም ጉዳዩን በታዛቢነት እንዲከታተለው ጠይቀዋል። ድሮም፤ አሁንም ወደፊትም የኦሮሞ ህዝባዊ ኮንግረስ፤ ሰላማዊ ትግሉን እንደሚቀጥል ያስታወቁትን አቶ ኦልባናን ፣ ተክሌ የኋላ በስልክ አነጋግሮአቸዋል።
ተክሌ የኋላ
ነጋሽ መሀመድ