የእትዮጵያ ፖለቲካ ከአቶ መለስ በኋላ
ሐሙስ፣ ነሐሴ 17 2004ማስታወቂያ
ላለፉት 21 አመታት ኢትዮጵያን የመሩት የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት በአገሪቱም ሆነ በአካባቢው አገራት ላይ ከፍተኛ አንድምታ እንደሚኖረው ክራይስ ግሩፕ አስታወቀ ። መቀመጫውን ብራሰልስ ቤልጅየም ያደረገው የፖለቲካ ቀውስና ግጭቶችን የሚተነትነው ክራይስስ ግሩፕ የተባለው ድርጅት ኢትዮጵያ ከአቶ መለስ በኋላ ሲል ባወጣው ዘገባ አተ መለስን የሚተካው አመራር ከዚህ ቀደም የተገለሉ ቡድኖችን ለማሳተፍ ጥረት ማድረግ እንደሚገባው አሳስቧል ። ለጋሽ አገራትም በተተኪው መሪ ላይ ትክክለኛ አቋም እንዲይዙም ጠይቋል ። የድርጅቱን ባልደረባ ያነጋገረው የብራሰልሱ ዘጋቢያችን ገበያው ንጉሴ ቀጣዩን ዘገባ ልኮልናል ።
ገበያው ንጉሴ
ሂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ