የእስራኤል 70ኛ ዓመት ምስረታ ቤተ-እስራኤላዉያን
ረቡዕ፣ ሚያዝያ 10 2010ማስታወቂያ
በሺዎች በሚቆጠሩ በእስራኤል ከተሰዉት መካከል በአሸባሪ ጥቃትና በጥበቃ ስራ ላይ ሳሉ በደረሰ አደጋ የተሰዉ ቤተ-እስራኤላዉያንም ይገኙበታል። ዛሬ ሲደረግ የዋለዉ የመታሰብያ ሥነ-ስርዓት ምሽት ላይ የተሰዉ የእስራኤል ጀግኖችን በሚከብረዉ ችቦ ማብራት ስነስርዓት ይጠቃለላል። በነገዉ እለት በተለያዩ ትርዒቶች እንደሚከበር ተገልፆአል። በሌላ በኩል ሃገራችንን ወረዋል ሲሉ በሚከሱት ፍልስጤማዉያን ጥያቄ የእስራኤል ሰባኛ ዓመት ምስረታ ጥላ አጥልቶበት ይገኛል። በእስራኤል ስለ 70ኛ ዓመት ምስረታ ክብረ በዓል በተመለከተ በእስራኤል የቀድሞዉ የአፍሪቃ ስደተኞች ጉዳይ ቢሮ ዋና ተጠሪን አቶ ዮሃንስ ባዩን አነጋግረንናል። አቶ ዮሃንስ ስለሚታየዉ ድባበብ በመግለፅ ቃለ ምልልሱን ይጀምራሉ።
አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሐመድ