የኤርትራ ክስ፣ የኢትዮጵያ ምላሽና የፖለቲካ ተንታኝ
ሰኞ፣ ታኅሣሥ 26 2002ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ የኮምኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት የመንግስት ቃል አቀባይ አቶ ሽመልስ ከማል ለዴይቼ ቬለ በሰጡት አስተያየት የኤርትራ ተቃዋሚዎች በኤርትራ ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውን እያስታወቁ ኤርትራ ኢትዮጵያን በጥቃቱ መወንጀሏ የውስጥ ችግር እንዳለባት ይጠቁማል ሲሉ አስታውቀዋል ። የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ አሊ አብዶ በበኩላቸዉ ኤርትራ ገደልኩና ማረኩ ስለምትላቸዉ የኢትዮጵያ ወታደሮች እንዲሁም ተያያዥ ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል። በሁለቱ አገራት መካከል የተከሰተዉ ሁኔታ በማስመልከት የአገራቱን ይዞታ በቅርቡ የሚያዉቁትን የኖርዌይ ዓለም ዓቀፍ ህግና ፖሊሲ ቡድን ባልደረባ የሆኑት ዶክተር ኼቲል ትሩንቨል ተጠይቀዋል።
ዘገባዎቹን በቅደም ተከተል ማዳመጥ ይችላሉ።
ታደሰ እንግዳዉ/ ሂሩት መለሠ/ ሸዋዬ ለገሠ