1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኤርትራና ኢትዮጵያ ስደተኞች ሰቆቃ

ረቡዕ፣ መጋቢት 25 2005

በሱዳን የተጠለሉ ኤርትራውያን ስደተኞች በአስግድዶ መድፈር በዱላ ድብደባ፣ በእሥራትና በመሳሰለው የግፍ ተግባር ከመሠቃየታቸውም፤ አንዳንዴም ተገደው ወደ ግብፅ ከተሻገሩ በኋላ በሲና ልሳነ-ምድር ይገደላሉ። አንዳንዶችም ፤ እንዲለቀቁ ጠቀም ያለ ገንዘብ

https://p.dw.com/p/1894o
ምስል Reuters

እንዲከፍሉ ተወጥረው ይያዛሉ ። በየጊዜው ሰፋ ያሉ የሰቆቃ ዘገባዎች የሚደርሱት ዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት AI በዛሬው ዕለትም በዚህ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሰጥቷል። በድርጅቱ፤ የኢትዮጵያና ኤርትራ የሰብአዊ መብት ጉዳዮትች ተመራማሪ የሆኑት ክሌር ቤስተን--

በሱዳንና በግብፅ ፍዳ ስለሚያዩ ፣ ግፍ ስለሚፈጸምባቸው፣ በአሠቃቂ ሁኔታ ስለሚገደሉ ኤርትራውያንና ኢትዮጵውያን መከራ ፣ በየጊዜው ብዙ ይነገራል፤ ከምሥራቃዊው ሱዳን ሸጋረብ መጠለያ ጣቢያ AI ስለደረሰው ዘገባ ወ/ት ክሌር ቤስተን እንዲህ አብራርተዋል።

«ለ2 ዓመታት ያህል በምሥራቃዊው ሱዳን በሸጋረብ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ፣ የፖለቲካ ተገን ጠያቂዎችና ስደተኞች ታፍነው እንደሚወሰዱ፣ ተገደው ወደግብፅ እንዲሻገሩና ከዚያም ሲና በረሃ፣ ታግተው ፣ ከቤተሰቦቻቸው ማስለቀቂያ በዛ ያለ ገንዘብ እንዲከፍሉ እንደሚገደዱ መስማታችን አልቀረም ። ያገቷቸው ሰዎች ፍጹም ኢሰብአዊ የሆነ የግፍ ተግባር እንደሚፈጽሙባቸው፣

13 Ägypter bei Angriff an Grenze zu Israel getötet KARTE GRENZE ISRAEL ÄGYPTEN
ምስል DW

እንደሚደበደቡ፣ ናፍጣ በሰውነታቸው ላይ እየደፉ እንደሚያቃጥሏቸው፤ በኤሌክትሪክ ገመድ መግረፍና በሰቅጣጭ የኤሌክትሪክ ንዝረት እንደሚያሠቃዩአቸው፣ ሴቶችም ፣ ወንዶችም እንደሚደፈሩ፣ ከቤተሰብም ሆነ ቤተዘመድ ፤ ሰዎቹን ለማስለቀቅ፣ የሚጠየቀው ገንዘብም ከ 30 ሺ እስከ 40 ሺ የአሜሪካ ዶላር መሆኑን ከዘገባው ተገንዝበናል።»

አሁን ያወሱልን ዘግናኝ ድርጊት ባለፉት ዓመታትም፣ በተደጋጋሚ የተፈጸመ ነውና AI ም ሆነ ሌሎች መሰል ድርጅቶች፣ ይህ ሰቆቃ እንዲገታ ምን ያደርጋሉ?

« በዛሬው ዕለት ስለሁኔታው መግለጫ ሰጥተናል። በአንዳንድ እጅግ ዘግናኝ በሆኑ የሰብአዊ መብት ይዞታዎች ላይ ነው ማብራሪያ የሰጠነው። በመግለጫችንም ላይ በዛ ያሉ ሊፈጸሙ ይገባል ብለን ያሰብናቸውን ሐሳቦችና ማሳሳቢያዎች፤ ለሚመለከታቸው መንግሥታት አቅርበናል። ----»

ተክሌ የኋላ

አርያም ተክሌ