የኤሌክትሪክ ችግር በኢትዮጵያ
ረቡዕ፣ ጥቅምት 27 2006ማስታወቂያ
በመላው ኢትዮጵያ ተደጋግሞ የሚደርሰው የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ በዕለት ተዕለት ኑሮና የሥራ ሂደት ላይ እክል እንደሚያስከትል ህብረተሰቡ አማረረ። አስቀድሞ ሳይነገር በሚደርስ የኤሌክትሪክ መጥፋት ምክንያት የአገልግሎት ሰጭ ድርጅቶች ሥራ በተደጋጋሚ እንደሚስተጓጓልና በዕለት ተዕለት ኑሮም በኤሌክትሪክ ማብሰያዎች መጠቀም አስቸጋሪ እየሆነ መምጣቱን ዶቼቬለ የጠየቃቸው አስተያየት ሰጭዎች ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን በበኩሉ የኤሌክትሪክ መቆራረጥ የደረሰው በተፈጥሮአዊና ሰው ሠራሽ ችግሮች እንደነበርና አሁን ግን ችግሩ እየተቃለለ መሆኑን አስታውቋል። ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሄር ከአዲስ አበባ ዝርዝር ዘገባ አለው።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሄር
ሂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ