የኢትዮጵያ ጦር እና አሚሶም
ረቡዕ፣ ጥር 14 2006ማስታወቂያ
ሶማሊያ የሠፈረዉ የኢትዮጵያ ጦር እዚያዉ በሠፈረዉ የአፍሪቃ ሕብረት ሠራዊት (AMISOM) ዕዝ ሥር ዛሬ በይፋ ተጠቃለለ።ኢትዮጵያ የሶማሊያዉን አክራሪ ደፈጣ ተዋጊ ቡድንን አሸባብን እንዲወጋ ከሁለት ሺሕ ሰወስት ጀምሮ ዳግም ሶማሊያ ዉስጥ ያሰፈረችዉ ጦር እስከ ዛሬ በራሱ ወጪ፥ ዕዝ እና መዋቅር ሲንቀሳቀስ ነበር።የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት እንዳስታወቁት አሁን ጦሩ በአሚሶም ዕዝ ሥር የተጠቃለለዉ በጋራ መንቀሳቀሱ የጦሩን ተዕልኮ ከግብ ለማድረስ ጠቃሚ በመሆኑ ነዉ።የወጪ ጉዳይም ከግምት የሚገባ ነዉ።አሚሶምን የተቀየጠዉ የኢትዮጵያ ጦር አራት ሺሕ ወታደሮች አሉት።ሥለ እርምጃዉ የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲን በስልክ አነጋግሬቸዋለሁ።
ነጋሽ መሐመድ
ሒሩት መለሠ