1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ የመብት ይዞታና የአንድ የውሁዳን ሕዝቦች ተቆርቋሪ ድርጅት ጥያቄ

ረቡዕ፣ መስከረም 4 2009

የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ፣ለሰብአዊ መብት መከበር ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ አይደለም ሲል በጀርመን የሚገኘዉ ለአደጋ የተጋለጡ ሕዝቦች ተሟጋች ድርጅት፣ «ጌዘልሻፍት ፊውር በድሮተ ፈልከር» ገለጠ።

https://p.dw.com/p/1K242
Gesellschaft für bedrohte Völker Logo Grafik

[No title]

የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ ከትናንት ማክሰኞ ዕለት፣ 13.09.2016 ጀምሮ በጀኔቫ ስዊትዘርላንድ 33ኛዉን መደበኛ ስብሰባ በማካሄድ ላይ ነው። ይህን አስመልክቶ «ጌዘልሻፍት ፊውር በድሮተ ፈልከር» ባወጣዉ መግለጫ እንዳስታወቀው፣ በተለይ በኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ እየደረሰ ያለዉን የሰብአዊ መብት ጥሰት የመንግሥታቱ ምክር ቤት አለማዉገዙና በገለልተኛ ወገን እንዲጣራ አለማድረጉ ጉባኤዉ ለሰብዓዊ መብት መከበር ያለዉ ትኩረት አናሳ ነዉ።

ፀሐይ ጫኔ

አርያም ተክሌ