የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር መግለጫ
ሐሙስ፣ ሰኔ 8 2009ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ መንግሥት፤ ከሳዑዲ አረቢያ የሚመለሱ ዜጎቹን ለማስተናገድ መቸገሩን ዛሬ በይፋ አመነ።የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ እንዳሉት 82 ሺሕ ኢትዮጵያዉያን ወደ ሐገራቸዉ ለመግባት ተመዝግበዋል።ይሁንና የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት የሰጠዉ ቀነ-ቀነ-ገደብ 12 ቀናት ሥለቀሩት፤ ኢትዮጵያዉያኑን በሙሉ በዚሕ ጊዜ ዉስጥ ማጓጓዝ አይቻልም።ቃል አቀባዩ በጋዜጣዊ መግለጫቸዉ የኢትዮጵያና የኤርትራን ዉዝግብ ጨምሮ ከጋዜጠኞች ለተነሱ የተለያዩ ጥያቄዎች መልስና ማብራሪያ ሰጥተዋል።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚያአብሔር መግለጫዉን ተከታትሎት ነበር።
ዮሐንስ ገብረ እግዚያአብሔር
ነጋሽ መሐመድ
አዜብ ታደሰ