1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ወታደሮች በሶማሊያ መቆየት

ሰኞ፣ ሰኔ 18 2004

ኢትዮጵያ ወደ ሶማሊያ የላከቻቸውን ወታደሮች በሶማሊያ እንደምታቆይ ሮይተርስ የዜና ወኪል ያለፈው ቅዳሜ ባወጣው ዘገባ ገለፀ።

https://p.dw.com/p/15LBB
Ethiopian troops travel on the back of a lorry as they make their way to the former American Embassy in Mogadishu, Somalia, Friday, Dec. 29, 2006. The leader of Somalia's Islamic political movement vowed Friday to continue the fight against Ethiopia, which lent key military support to the government in a campaign that saw the Islamic militia retreat from the capital a day earlier (AP Photo/Mohamed Sheikh Nor)
ምስል AP

ኢትዮጵያ በህዳር ወር ነበር ታንኮች እና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወታደሮቿን ወደ ሶማሊያ የላከችው። የተልዕኮው አላማ በሶማሊያ የሚገኘውን አማፂ ቡድን አሸባብን በመውጋት በአጭር ጊዜ ውስጥ ሶማሊያን ለቆ እንዲወጣ ለማድረግ ነበር። ይሁንና ሮይተርስ የዜና ወኪል ያለፈው ቅዳሜ ባወጣው ዘገባ፤ ኢትዮጵያ ወታደሮቿን የአፍሪቃ ህብረት እንዳለው በሚያዚያ ወር መጨረሻ ሳይሆን በሰኔ ወርም አላስወጣችም። እንደውም ተልዕኮዋቸው እንደሚራዘም አመልክታለች። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ኢትዮጵያ ወታደሮቿን በሶማሊያ የምታቆይበትን ምክንያት ለዶይቸ ቬለ ገልፀዋል።

ልደት አበበ

ተክሌ የኋላ