የኢትዮጵያ ከሶማልያ መውጣት
ረቡዕ፣ ጥር 6 2001ማስታወቂያ
እንደ ወራሪ ኃይል ይታዩ ለነበሩት ኢትዮጵያውያን ወታደሮች የሶማልያ የሽግግር መንግስት ደማቅ አሸኛኘት አድርጎላቸዋል። የሽግግሩ መንግስት ተቃዋሚ የሆኑት የሶማልያ ዳግም ነጻነት ለዘብተኛ ሙስሊሞችም ሚሊሺያዎች የኢትዮጵያ ወታደሮች የለቀቁዋቸውን ሰፈሮች ከሌሎች ተፎካካሪ ተቀናቃኞቻቸው ጋር ተዋግተው መያዛቸው ተገልጾዋል። አንዳንድ የዚሁ ኅብረት ከፍተኛ አባላት አሁን በምክር ቤቱ አፈ ጉባዔና ባለፈው ወር ስልጣናቸውን የለቀቁትን ፕሬዚደንት አብዱላሂ ዩሱፍን በተኩት በተጠባባቂ ፕሬዚደንት ሼክ አደን ማዶቤ የሚመራውን የሽግግር መንግስት ተቀላቅለዋል።