1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ኤኮኖሚ ይዞታና የውጭ ምንዛሪ እጥረት

እሑድ፣ ሚያዝያ 28 2010

የኢትዮጵያ ኤኮኖሚ ምንም እንኳን ባለፈው ዐሥርተ ዓመት ዓመታዊ 10% ኤኮኖሚያዊ እድገት ማስመዝገቧ ቢነገርም፣ በወቅቱ ችግሮች እንዳሉበት ይነገራል። ችግሩ የእድገቱን ሂደት ሊገቱት እንደሚችሉ ባለሙያዎች እያሳሰቡ ነው።  

https://p.dw.com/p/2xCK7
Symbolbild Währungen Währungskrieg
ምስል imago/Birgit Koch

ኢትዮጵያ እና የኤኮኖሚ ይዞታዋ

የውጭ ንግድ እንደሚፈለገው አለማደጉ፣ በሀገር ውስጥ ቁጠባ እና በኢንቬስትመንት መካከል ያለው ልዩነት ግልጽ አለመሆኑን፣ ከሁሉም በላይ ግን የውጭ ምንዛሪ እጥረት እንደ ዋነኛ ችግር ይጠቀሳሉ። አዲሱ የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶክተር አብይ አህመድ በሀገሪቱ በተለይ ባለፉት ሶስት ዓመታት ለታየው የፖለቲካ ቀውስ መፍትሔ በማስገኘት በቀውሱ ሰበብ ችግር የገጠመው የምጣኔ ሀብት ይዞታ የሚሻሻልበትን ዘዴ ያስገኙ ይሆናል በሚል ብዙዎች ተስፋ አድርገዋል።  ጠቅላይ ሚንስትሩ ባጠቃላይ ኤኮኖሚውን ለማነቃቃት እስካሁን የጠቆሙት የፖሊሲ አቅጣጫም ግን የለም። የሳምንቱ ውይይታችን በኢትዮጵያ ኤኮኖሚ ይዞታ እና በተለይ በውጭ ምንዛሪ እጥረት ላይ አትኩሯል።

ሙሉ ውይይቱከታች የድምፅ ማዕቀፉ ውስጥ ይገኛል።

አርያም ተክሌ

ማንተጋፍት ስለሺ