የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ጉብኝት በበርሊን
ማክሰኞ፣ ኅዳር 23 2007ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ሐይለ ማርያም ደሳለኝ የሚመሩት የኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ የመልዕክተኞች ቡድን ጀርመንን ለመጎብኘት ነገ በርሊን ይገባል።ሥለ ጉብኝቱ አላማና ሒደት እንዲያስረዱን የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ የኮሚኒኬሽን መስሪያቤት እና በበርሊን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባለሥልጣናትን ከትናንት ጀምሮ በሥልክ ለማነጋገር ሞክረን ነበር።ነገር ግን በሥልክ ያገኘናቸዉ ፍቃደኞች አይደሉም።ሌሎቹ ደግሞ አልተገኙም። የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ሐይለ ሚካኤል እንደሚለዉ ግን በጠቅላይ ሚንስትር ሐይለ ማርያም የሚመራዉ ቡድን የጀርመንኗን መራሒተ-መንግሥት አንጌላ ሜርክልን ጨምሮ የተለያዩ የጀርመን ባለሥልጣናትንና ባለሐብቶችን ለማነጋገር ቀጠሮ አለዉ።ጀርመን የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን፤ የኢትዮጵያ ወዳጆችና የሠብአዊ መብት ተሟጋቾች ባንፃሩ እዚያዉ በርሊን ዉስጥ ተቃዉሞ ሠልፍ ለማድረግ አቅደዋል።
ይልማ ሐይለ ሚካኤል
ነጋሽ መሐመድ