የኢትዮጵያዉያን ሐጃጆች አቤቱታ
ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 1 2002ማስታወቂያ
ለሐጅ ወደ ሥዑዲ አረቢያ የተጓዙ ኢትዮጵያዉያን ምዕመናን ትኬት የሸጠላቸዉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ «ወደ ሐገራችን አልመልስም ብሎን በሰዉ ሐገር እየተንገላታን፥ እየተራብን፥ እየተጠማን ነዉ» በማለት አማረሩ።አራት ሺሕ የሚገመቱት ምዕመናን ሊመልሳቸዉ የሚገባዉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የፀሎት ጊዜዉ ካበቃ ከአስራ-አምስት ቀናት በሕዋላ አሁንም ወደ ሐገራቸዉ ሊመልሳቸዉ ፈቃደኛ አይደለም።የአየር መንገዱን ባለሥልሥልጣናት ለማነጋገር በተደጋጋሚ ያደርገነዉ ሙከራ አልተሳካም። የጂዳዉ ወኪላችን ነብዩ ሲራክ ዝር ዝሩን አጠናቅሮታል።
ነብዩ ሲራክ
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ