የኢትዮጵያና የደቡብ ሱዳን ስምምነት
ዓርብ፣ የካቲት 17 2009ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ መንግስት፤ በርስ በርስ ጦርነትና በረሐብ ከተመሰቃቀለችዉ ከደቡብ ሱዳን መንግሥት ጋር የተለያዩ ምጣኔ ሐብታዊ እና ሙያዊ ሥምምነቶችን ተፈራረመ።አዲስ አበባን የጎበኘዉ በፕሬዝደንት ሳልቫ ኪር የተመራዉ የደቡብ ሱዳን ከፍተኛ የመልዕክተኞች ጓድ ከኢትዮጵያ አቻዎቹ ጋር የተፈራረመመዉ ሥምምነት የንግድ፤የመንግድ ሥራ፤ የኤሌክትሪክ ኃይል ሺያጭና የጋዜጠኝነት ሥልጠናን የሚያካትት ነዉ።ደቡብ ሱዳን እንደ ጎርጎሪያኑ አቆጣጠር ከ2013 ጀምሮ በርስበርስ ጦርነት እየወደመች ነዉ።አሁን ደግሞ በመቶ ሺሕ የሚቆጠር ሕዝቧ ለገዳይ ረሐብ ተጋልጧል።ፕሬዝደንት ሳልቫ ኪር በአዲስ አበባ ያደረጉትን ጉብኝት ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ተከታትሎታል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሰ