የኢትዮጵያና ኤርትራዉያን ወዳጅነት መድረክ8 የካቲት 2005ዓርብ፣ የካቲት 8 2005የኢትዮጵያና ኤርትራዉያን ወዳጅነት መድረክ በካሊፎርኒያ ግዛት ዉስጥ ከምትገኘዉ የሳንሆዜ ከተማ ዛሬ የእዉቅና እና የክብር ሽልማት እንደሚበረከትለት ተገለፀ።https://p.dw.com/p/17fC2ምስል picture alliance / Arco Images GmbHማስታወቂያ መድረኩ ለዚህ እዉቅናና ሽልማት የበቃዉ የሁለቱን ሀገራት ህዝቦች በሰላምና በፍቅር ዙሪያ ለማሰባሰብ ባደረጋቸዉ ጥረቶች መሆኑ ተገልጿል። ከመድረኩ ሌላ አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን ወይም ቴዲ አፍሮ የክብር ሽልማት እንደሚበረከትለት ታዉቋል። ዝርዝሩን የዋሽንግተን ዲሲዉ ወኪላችን አበበ ፈለቀ ልኮልናል። አበበ ፈለቀ ሸዋዬ ለገሠ ነጋሽ መሐመድ