የኢሕዲግ ሥብሰባና የሥልጣን ሽግግር
ዓርብ፣ መስከረም 4 2005ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ገዢ ፓርቲ የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሐዲግ) ምክር ቤት በሞት የተለዩትን የግንባሩን ሊቀመንበርና የኢትዮጵያን ጠቅላይ ሚንስትር አቶ መለስ ዜናዊን የሚተካዉን ፖለቲከኛ ለመምረጥ ዛሬ ተሰብስቧል።ምክር ቤቱ ነገንም ጭምር በሚያደርገዉ ሥብሰባዉ የሚወስነዉና የሚመርጠዉ ሰዉ የወደፊቱን የሐገሪቱን ፖለታዊ ሒደት የሚበይን ነዉ ተብሎ ይጠበቃል።የኢትዮጵያ ጉዳይ የፖለቲካ አጥኚ ዶክተር ቶቢያስ ሐግማን እንደሚሉት ግን ኢሕአዴግ በጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ከነበረዉ የተለየ ፖለቲካዊ መርሕ ይቀይሳል ተብሎ አይጠበቅም።ተቋዋሚ ፖለቲከኞችን የሚያሳትፍ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትም ይዘረጋል ተብሎ አይጠበቅም።የዋሽግተኑ ወኪላችን አበበ ፈለቀ ዶክተር ሐግማንን አነግሮ ያጠናቀረዉ ዘገባ አለዉ።
አበበ ፈለቀ
ነጋሽ መሐመድ
ሒሩት መለሰ