የአፍሪቃ ቀን በአምስተርዳም
ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 8 2011ማስታወቂያ
ባለፈዉ ቅዳሜ አምስተርዳም-ኔዘርላንድስ ዉስጥ የተከበረዉ የአፍሪቃ ቀን በአፍሪቃ የፖለቲካ፣ማኅበራዊ እና የአየር ንብረት ለዉጦች ላይ ተወያይቶአል። ከ 40 በላይ ድርጅቶች የተሳተፉበት፤ ይህ ዝግጅት ከ 12 እንስከ 13 ሺህ እድምተኞችን ያሳተፈ መሆኑን የሚናገሩት የዝግጅቱ አስተባባሪ፤ዓላማዉ የአፍሪቃን ትክክለኛ ገጽታ ማስገንዘብ እና የአዉሮጳ መንግሥታት የልማት ፖሊሲዎችም ሕዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ እንዲሆኑ ለማግባባት ነዉ ብለዋል። በእለቱ ከነበሩት ዝግጅቶች አንዱ የኢትዮጵያን ሽግግር መረዳት በሚል የቀረበዉ የፓናል ዉይይት ነበር።
ገበያዉ ንጉሴ
ነጋሽ መሐመድ
ማንተጋፍቶት ስለሺ