የአፍሪቃና የአውሮፓ ህብረት ጉባኤ ፍፃሜ
ሰኞ፣ መጋቢት 29 2006ማስታወቂያ
የአፍሪቃና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች ይበልጥ ተቀራርበው ለመሥራት ቃል ገቡ ።ብራሰልስ ቤልጂግ ውስጥ ለ2 ቀናት የተካሄደው 4ተኛው የሁለቱ ክፍለ ዓለማት መሪዎች ጉባኤ ሲጠናቀቅ መሪዎቹ የጋራ ችግሮቻቸውን በጋራ ለመፍታትም ፅኑ አቋም እንደያዙ አስታውቀዋል ። ሆኖም ሁለቱ ወገኖች የግብረሰዶማውያንን መብቶች በመሳሰሉ ጉዳዮች ላይ ግን መለያየታቸው አልቀረም ። በጉባኤው ላይ ከ50 የሚበልጡ የአፍሪቃ ሃገራትና የ28ቱ የአውሮፓ ህብረት አባል ሃገራት በመሪዎቻቸውና በከፍተኛ ልዑካኖቻቸው የተወከሉ ሲሆን የሌሎች ሃገራት መንግሥታትና የዓለም ዓቀፍ ድርጅቶች ተወካዮችም ተገኝተዋል ። የጉባኤውን ሂደት የተከታተለው የብራሰልሱ ዘጋቢያችን ገበያው ንጉሴ ዝርዝሩን ልኮልናል ።
ገበያው ንጉሴ
ሂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ