የአዴፓ መግለጫ
ቅዳሜ፣ ሰኔ 22 2011ማስታወቂያ
የድርጊቱ ፈጣሪዎች ያላቸውን በቁጥጥር ስር እያዋለ መሆኑን የገለጸው አዴፓ፤ መንግሥት እና ድርጅቱን አደጋ ላይ የሚጥሉ አሉባልታዎችና ያልተጨበጡ መረጃዎች እየተነዙ በመሆኑ ህዝቡ ጉዳዩን እንዲመዝንም አሳስቧል። የአማራ ዴሞክራሲዊ ፓርቲ ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው አዴፓ ታጋይ መሪዎቹን ቢያጣም ራሱን አጠናክሮ የህብረተሰቡን ፍላጎት ለማሟላት ከምንጊዜውም በላይ ጠንክሮ ይሰራል ብሏል፡፡ የመፈንቅለ መንግስቱ ያነጣጣጠረው በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር፣ በአዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ ፅህፈት ቤት፣ በፖሊስ ኮሚሽን፣ ብዙሀን መገናኛ ድርጅትንና የግለሰቦችን ቤት ያነጣጠረ እንደነበርም መግለጫው አመልክቷል፡፡ ድርጊቱን የፀጥታ ሓይሉና ህብረተሰቡ ያከሸፈው መሆኑን የጠቀሰው መግለጫው በዚህም ድርጊቱን ለማክሽፍ የተባበሩትን ሁሉ አመስግኗል፡፡ከባሕር ዳር ወኪላችን ዓለምነው መኮንን አጭር ዘገባ ልኮልናል።
ዓለምነው መኮንን
ዓለምነው መኮንን