የአውሮፓ የስደተኞች አቀባበል መርህ
ሐሙስ፣ መስከረም 25 2004ማስታወቂያ
ቀድሞም በስደተኞች የተጨናነቁት ግሪክ ና ማልታ ከአረቡ ዓለም ህዝባዊ አብዮት በኋላ የሚጎርፈውን ስደተኛ የያዙበት መንገድ አሳዛኝ መሆኑን ስደተኞችም ሆነ አካባቢውን የጎበኙ የአውሮፓ ፖለቲከተኞች ጭምር የሚናገሩት ነው ። በዚህ ዓይነት ሁኔታ የሚሰቃዩትን ስደተኞች የተቀሩት የአውሮፓ ህብረት አባል ሃገራት እንዲያስጠጉ በተደጋጋሚ ቢጠየቁም እስካሁን አጥጋቢ መልሰ አልሰጡም ። የችግሩን አሳሳቢነት በማጉላት ለአውሮፓ መንግሥታት ተጨማሪ ጥሪ ያስተላለፈ ስብሰባ ትናንት ብራሰልስ ቤልጂግ በአውሮፓ ህብረት ፓርላማ ተካሂዷል ። ስብሰባውን የተከታተለውን የብራሰልሱ ዘጋቢያችን ገበያው ንጉሴን ስቱድዮ ከመግባቴ በፊት በስልክ አነጋግሬዋለሁ ።
ሂሩት መለሰ
ገበያው ንጉሴ
አርያም ተክሌ