1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአውሮጳ ህብረት እና የተገን አሰጣጡ ፖለቲካው

ማክሰኞ፣ መስከረም 12 2002

የአውሮጳ ህብረት አባል መንግስታት የሀገር ውስጥ አስተዳደር ሚንስትሮች በህገ ወጥ መንገድ ወደአውሮጳ ስለሚፈልሱና የፖለቲካ ተገን ስለሚጠይቁ ሰዎች ትናንት በብራስልስ ምክክር አካሄዱ።

https://p.dw.com/p/JmG8
ህግ ወጥ ስደተኞች በላምፔዱዛ፤ ኢጣልያምስል dpa

የአውሮጳ ህብረት ኮሚስዮን ወደሀገራቸው ሊመለሱ ከማይችሉት መካከል ጥቂቶቹን ለመቀበል በስብሰባው ላይ ያቀረበውን ሀሳብ አባል ሀገራቱ ሚንስትሮች ደግፈው መቀበላቸውን ወቅታዊው የህብረቱ የሚንስትሮች ምክር ቤት ፕሬዚደንትን ስልጣን የያዘችው የስዊድን ሀገር አስተዳደር ሚንስትር ቶቢያስ ቢልስትሮም እና የህብረቱ ኮሚስዮን የፍትህና ደህንነት ጉዳይ ምክትል ኮሚሽነር ዣክ ባሮት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አስረድተዋል። ከዚህ ሌላም ስደተኞቹ፡ ብቻቸውን ወደአውሮጳ የሚገቡ ልጆች ጭምር፡ ከሚመጡባቸው ሀገሮች ጋር ምክክር እንደሚያስፈልግ ባለስልጣናቱ አስታውቀዋል።

ገበያው ንጉሴ/አርያም ተክሌ

ሸዋዬ ለገሠ