የአዉሮጳ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ
ዓርብ፣ ሰኔ 17 2003ማስታወቂያ
የአዉሮጳ ሕብረት አባል ሐገራት የመሪዎች ጉባኤ በሰወስት አበይት ጉዳዮች ላይ ለሁለት ቀን መክሮ ዛሬ ተጠናቅቋል። ከትናንት ጀምሮ ብራስልስ-ቤልጅግ ዉስጥ የመከሩት የሃያ-ሰባቱ አባል ሐገራት መሪዎች የአዉሮጳን ምጣኔ ሐብት ክፉኛ ያሰጋዉን የግሪክን ምጣኔ ሐብት ከከፋ ዉድቀት ለማዳን ተጨማሪ እርዳታ ለመስጠት ተስማምተዋል።ወደ አዉሮጳ ሥለ ሚፈልሱ ስደተኞችና የአረብ ሐገራትን ሕዝባዊ አብዮት በተመለከተም የተለያዩ ዉሳኔዎችን አሳልፈዋል።ጉባኤዉ ከአንድ ሠዓት በፊት ተጠናቋል።ሥለ ጉባኤዉ ሒደትና ዉሳኔ የብራልሱን ወኪላችን ገበያዉ ንጉሴን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።
ገበያዉ ንጉሴ
ነጋሽ መሐመድ
ሂሩት መለሠ