የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የሰነዘረዉ ክስ
ማክሰኞ፣ ኅዳር 2 2007ማስታወቂያ
ዶቼ ቬለ ያነጋገራቸዉ የፓርቲዉ የብሄራዊ ምክር ቤት አባል እና የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዘካርያስ የማነ ብርሃን እንደገለፁት በሀገሪቱ ሊደረግ የታቀደዉን ብሔራዊ ምርጫ አስመልክቶ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ የሚሰነዘረዉ ወከባ መንግስት የፖለቲካ እንቅስቃሴዉን ለመቆጣጠር ሆነ ብሎ እያደረገ ያለዉ ተግባር ነዉ።
እንደ ሁልጊዜዉ ሁሉ አሁንም የፓርቲዉ አባላት ላይ እስራት፤ እንግልትና ወከባ ይፈፀምባቸዋል፤ ያሉት የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የብሄራዊ ምክር ቤት አባልና የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዘካርያስ የማነ ብርሃን ለሀገሪቱ ዘርፈ ብዙ ፖለቲካዊ ችግሮች እስርና ወከባ መፍትሄ አይሆንም የሚል መግለጫ ፓርቲያቸዉ ማዉጣቱን ገልፀዋል። ይህ ደግሞ በመጪዉ ግንቦት በሚደረገዉ ብሄራዊ ምርጫ ላይ ፓርቲዉ እንዳይሳተፍ የተወሰደ ርምጃ ነዉ ያሉት አቶ ዘካርያስ የማነ ብርሃን። ሙሉ ቃለ-ምልልሱን የድምፅ ማድመጫ ማዕቀፉን በመጫን ይከታተሉ።
አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሃመድ