የአቶ አንዱዓለም አራጌ መደብደብ
ማክሰኞ፣ የካቲት 13 2004ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ አንድነት ለፍትሕና ለዲሞክራሲ ፓርቲ የታሰረዉ የፓርቲዉ ከፍተኛ ባለሥልጣን አቶ አንዱዓለም አራጌ በሌላ እስረኛ መደብደባቸዉ ፖለቲካዊ እድምታ አለዉ በማለት ድርጊቱን አወገዘ።ባለሥልጣናቱ እንዳሉት ድብደባዉ በቁጥጥር ስር የሚገኙ ዜጎች ደሕንነት እንዲጠበቅ የሚደነግገዉ የሐገሪቱን ሕገ-መንግሥት የመንግሥትና የወሕኒ ቤቱ ባለሥልጣናት መጣሳቸዉን አመልካች ነዉ።አንዱአለምን የደበደበዉ ግለሠብ በነብስ ማጥፋት ወንጀል ሞት ተፈርዶበት ኃላ ቅጣቱ ወደ እድሜ ልክ እስራት የተቃለለት ግለሰብ እንደሆነ የጠቀሱት የፓርቲዉ መሪዎች፥ያልተፈረደበትን ተጠርጣሪ ከተፈረደበት ወንጀለኛ ጋር ማሳር ራሱ ሕገ-ወጥ ነዉ። የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ታደሰ እንግዳዉ ዝር ዝር ዘገባ ልኮልናል።
ታደሰ እንግዳዉ
ነጋሽ መሃመድ
አርያመ ተክሌ