የአተት በሽታ ስርጭት እና መከላከያው ርምጃ
እሑድ፣ ነሐሴ 22 2008ማስታወቂያ
የአተት ስርጭት በአማራ፣ በትግራይ፣ በአዲስ አበባ፣መታየቱ ከፌዴራል ጤና ጥበቃ ሚንስቴር የወጣ መረጃ አሳይቶዋል። ቀደም ሲልም ደቡብ፣ በኦሮሚያ እና በሶማሌ ክልሎች ተከስቶ የነበረው አሁን ወደ ሌሎች ክልሎች ተከስቶ እንደነበር ይታወሳል። መንግሥት ከስድስት እስከ አስር ሰዎች እንደሞቱ ተናግሮዋል፣ የተመድ ያወጣው መዘርዝር እንደሚያሳየው ደግሞ በሽታው ቡብ፣ በኦሮሚያ እና በሶማሌ ክልሎች ብቻ 19 ሰዎች ሕይወት አጥፍቶዋል። ይኸው የአተት በሽታ ስርጭት ተደጋግሞ መከሰቱ ሕዝቡን ማሳሰቡ አልቀረም። የአተት በሽታን ስርጭት ማስቆም ስላልተቻለበት ምክንያት እና ስለመከላከያው ርምጃ ውይይት አካሂደናል።
አርያም ተክሌ
ልደት አበበ