የአረና እና ታድ መግለጫ
ሐሙስ፣ ሚያዝያ 10 2011ማስታወቂያ
በሰላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ የነበሩ አባላቶቼ ደጋፊዎቼ ታሰሩ ሲል ዓረና ትግራይ ለሉዓላዊነትና ዴሞክራሲ ገለፀ፡፡ ፓርቲው ከትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር እንቅስቃሴ ጋር በጋራ በሰጠው መግለጫ በክልሉ ሰላማዊ የፓለቲካ እንቅስቃሴ ማድረግ አስቸጋሪ እየሆነብን ነው ብለዋል፡፡ለዶቼቬለ DW ስለጉዳዩ የጠየቃቸው ወጣቶቹ የታሰሩበት የኪውሀ አካባቢ ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ አልነበሩም፤ ፖሊስን ሲተነኩሱ በቁጥጥር ስር ውለዋል ሲል ተናግሯል። የመቀሌው ዘጋቢያችን ሚሊዮን ኃይለ ሥላሴ ዝርዝር ዘገባ አለው።
መቀሌ ኃይለ ሥላሴ
ኂሩት መለሰ
ማንተጋፍቶት ስለሺ