የአረና ትግራይ አቤቱታ
ረቡዕ፣ ግንቦት 12 2007ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ስር ከተሰባሰቡት ተቃዋሚ ፓርቲዎች አንዱ የሆነው አረና ትግራይ የምርጫ ቅስቀሳ ያካሂዱ የነበሩ አባላቶቹ ድብደባ እንደተፈጸመባቸው አስታወቀ ። ፓርቲው በትግራይ ምሥራቃዊ ዞን አፅቢደራ ወረዳ ትናንት ለቅስቀሳ በተሰማሩ አባላቶቹ ላይ በተካሄደ ድብደባ አንዳንዶቹ ለአካል ጉዳት መዳረጋቸውን ገልጿል ።አረና በድብደባው 10 አባላቱ መጎዳታቸውን ከመካከላቸው 3ቱ አሁንም ድረስ በህክምና ላይ እንደሚገኙም ተናግሯል ። የክልሉ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ ስለሁኔታው የደረሰው መረጃ እንደሌለ ለዶቼቬለ አስታውቋል ። የአዲስ አበባው ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሄር ዝርዝሩን ልኮልናል ።
ዮሀንስ ገ/እግዚአብሔር
ኂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ