የቱኒዝያ ስደተኞች በላምፔዱዛ
ሰኞ፣ የካቲት 7 2003ማስታወቂያ
የኢጣልያዋ ደሴት ላምፔዱዛ ካለፈው ሳምንት መጨረሻ አንስቶ በቱኒዝያ ስደተኞች እንደተጨናነቀች ነው ። ሁኔታው ያሳሰባት ኢጣልያ የቱኒዝያን መንግስትና የአውሮፓ ህብረት ትብብር እና እርዳታ እየጠየቀች ነው ። የአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳዮች ሃላፊ ካትሪን አሽተን ዛሬ የቱኒዝያን ባላሥልጣናት ቱኒስ ውስጥ ሲያነጋግሩ ከሚያነሷቸው ጉዳዮች ውስጥ ኢጣልያ የገቡት የቱኒዝያ ስደተኞች ጉዳይ ዋነኛው እንደሚሆን ተገምቷል ። ላምፔዱዛ ስለሚገኙት የቱኒዝያ ስደተኞች ሁኔታ የሮሙን ወኪላችንን ተክለ እዝጊ ገብረ እየሱስን በፊት በስልክ አነጋግሬዋለሁ ። ተክለ እዝጊ ገብረ እየሱስ ፣ ሂሩት መለሰ ተክሌ የኋላ