የተቃዋሚዎቹ ጠበቃ ተደበደቡ
ማክሰኞ፣ መጋቢት 1 2007ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ መንግሥት አሸባሪነትን ጨምሮ በተለያዩ ወንጀሎች ለከሰሳቸዉ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች፤ የሐይማኖት መሪዎችና ጋዜጠኞች ጥብቅና በመቆም የሚታወቁት አቶ ተማም አባ ቡልጎ ተደበደቡ።አቶ ተማም የተደበደቡት ዛሬ ከችሎት ወጥተዉ በመኪና ሲጓዙ ነዉ።ደብዳቢዉ ከአቶ ተማም ጋር አብሮ በነበሩና ባካባቢዉ ሰዎች ትብብር ተይዞ ሲጠየቅ የአዕምሮ በሽተኛ ይመስል የተለያዩ ፖለቲካዊ ርዕሶችን እያነሳ ይናገር እንደነበር የዓይን ምስክሮች አስታዉቀዋል።አቶ ተማም አይናቸዉ አካባቢ መጠነኛ ጉዳት ቢደርስባቸዉም ለክፉ የሚሰጥ አይደለም።ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ