የብራስልሱ ጉባኤ በጀርመኖች ዓይን
ዓርብ፣ መጋቢት 9 2008ማስታወቂያ
የጀርመን ፖለቲከኞችና የፖለቲካ ተንታኞች የአዉሮጳ ሕብረት አባል ሐገራት እና የቱርክ መሪዎች ብራስልስ ዉስጥ የሚያደርጉትን ድርድር ዉጤት በከፍተኛ ትኩረት እየተከታተሉት ነዉ።ድርድሩ አግባቢ ሥምምነት ላይ ከደረሰ የጀርመንዋ መራሒተ-መንግሥት አንጌላ ሜርክል ስደተኞችን በመቀበላቸዉ ከራሳቸዉ ፓርቲ ባለሥልጣንት የሚሰነዘርባቸዉን ተቃዉሞና ትችት በመጠኑም ቢሆን ይቀንስላቸዋል ነዉ የሚባለዉ።ያም ሆኖ ቱርክ ከግሪክ የሚጠረዙ ስደተኞችን እድትቀበል፤ ዜጎችዋ ያለ ቪዛ አዉሮጳ እንዲገቡ እና ለአዉሮጳ ሕብረት አባል ትሆን ዘንድ ድርድር እንዲጀመር ያቀረበችዉን ጥያቄ ሕብረቱ ከተቀበለዉ ለጀርመን ፖለቲከኞች ሌላ የዉዝግብ ርዕስ መሆኑ አይቀርም።የበርሊኑን ወኪላችንን ይልማ ሐይለ ሚካኤል ስቱዱዮ ከመግባቴ በፊት በስልክ አነጋግሩዋለሁ።
ይልማ ኃይለ ሚካኤል
ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሠ