የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ተፈናቃዮች አቤቱታ
ማክሰኞ፣ የካቲት 26 2011ማስታወቂያ
በርካቶችን ለመፈናቀል፣ ንብረት መውደም እና ሕይወት መጥፋት የዳረገውን የአካባቢውን የፀጥታ ችግር ለመፍታት በፌደራል የፀጥታ አካላት እና በሁለቱም ክልሎች የሚመራ የእዝ ጣቢያ ወይም ኮማንድ ፖስት መቋቋሙ ይታወሳል። የዕዝ ጣቢያው ከወር በፊት ባወጣው መግለጫ የሰው መፈናቀል ሙሉ በሙሉ መቆሙን፤ በከማሼ እና ሌሎችም አካባቢዎች የተዘጉ መንገዶች መከፈታቸውን ገልጾ ነበር። ሆኖም ግን ከተጠቀሱት አካባቢዎች የተፈናቀሉ የመንግሥት ሠራተኞች አሁንም ወደ ሥራ ገበታቸው መመለስ አለመቻላቸን ለDW አስረድተዋል። ዝርዝሩን ከአሶሳ ዘጋቢያችን ነጋሳ ደሳለኝ ልኮልናል።
ነጋሳ ደሳለኝ
ሸዋዬ ለገሠ
ተስፋለም ወልደየስ