የቡድን ስምንት ጉባኤ መክፈቻ
ረቡዕ፣ ሐምሌ 1 2001ማስታወቂያ
ቡድን ስምንት በመባል የሚጠሩት የዓለም ባለፀጋዎቹ መንግስታት መሪዎች ዓመታዊ ጉባኤ ዛሬ ላክዊላ ኢጣላያ ውስጥ በከፍተኛ የፀጥታ ጥበቃ ተጀምሯል ። መሪዎቹ በዛሬው የመጀመሪያው ቀን ጉባኤያቸው በተለይ በዓለም የምጣኔ ሀብት ቀውስና በአየር ንብረት ለውጥ እንዲሁም በኃይል ምንጭ ጉዳዮች ላይ አትኩረው ተወያይተዋል ። በዚህ ጉባኤ ላይ ዘጠነኛ መሪ ሆነው ለመካፈል የተጋበዙትና ትናንት ኢጣልያ የገቡት የቻይናው ፕሬዝዳንት ሁ ጂንታኦ ግን ሀገራቸው ውስጥ በተፈጥረው ግጭት ምክንያት ጉባኤውን ላይ ሳይገኙ ዛሬ ጠዋት ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል ። ተክለ እግዚ ገብረ እግዚአብሄር ከሮም በቡድን ስምንት ጉባኤ አጀንዳና ከጉባኤ በሚጠበቀው ውጤት ላይ ያተኮረ ዘገባ አለው ።
ተክለ እግዚ ገ/እየሱስ
ነጋሽ መሐመድ