የቡርቃ ዕገዳ በቤልጂግ
ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 26 2002ማስታወቂያ
ቡርቃ በአደባባይ እንዳይለበስ ለመከልከል በምክርቤት ደረጃ ድምፅ በመስጠት ቤልጂግ የመጀመሪያዋ አውሮፓዊት ሀገር ሆናለች ። የበርካታ ሙስሊሞች መኖሪያ በሆነችው በፈረንሳይ ደግሞ ማንነትን ይሸሽጋል የተባለውን ቡርቃን በሚለብሱ ላይ ከበድ ያለ ቅጣት የሚጥል ጠንካራ ህግ ተረቋል ። ሁለቱ ሐገራት ቡርቃን በአደባባይ እንዳይለበስ የወሰዱትና ለመውሰድ ያቀዱት ቁርጠኛ ዕርምጃ ፣ የአብዛኛው ዜጎቻቸው ድጋፍ ቢኖረውም ተቃውሞም አልተለየውም ። ቤልጂግና ፈረንሳይ በግንባር ቀደምትነት በቡርቃ እና ዓይንን ጭምር በሚከልለው በኒቃብ ላይ ሲዘምቱ ሌሎች የአውሮፓ ሐገራትም የነርሱን ፈለግ ለመከተል ዳር ዳር እያሉ ነው ። የዛሬው አውሮፓ እና ጀርመን ዝግጅታችንም በተለይ የቤልጂግ ምክር ቤት ባለፈው ሳምንት ቡርቃ መልበስ እንዲታገድ ባሳለፈው ውሳኔና በእገዳውን ደጋፊዎች እና ተቃዋሚዎች አስተያየት ላይ ያተኩራል ።
ሂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ