የሽብር ስጋት በኢጣልያ
ሰኞ፣ ነሐሴ 9 2008ማስታወቂያ
በሀገር አስተዳደሩ ሚንስትር አንጀሊኖ አልፋኖ ትዕዛዝ ተጠርጣሪ አሸባሪዎችን ከሀገሪቱ የማባረሩ ተግባር ተጠናክሮዋል። ባለፈው ቅዳሜ እንኳን በፒዛ ገዳዳ ሀውልት ላይ ጥቃት አቅደዋል በሚል የተጠረጠሩ በፑሊያ ፣ አንድሪያ የሚገኝ የአንድ መስጊድ ኢማም የሆኑ አንድ ቱኒዝያዊ ዋ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ አዘዋል። ካለፈው ዓመት ወዲህ የሀገር አስተዳደሩ ሚንስትር አንጀሊኖ አልፋኖ 109 ተጠርጣሪዎችን የማባረር ትዕዛዝ የፈረሙ ሲሆን፣ 43 ን እጎአ በ2016 ነው የፈረሙዋቸው። በኢጣልያ ስለተጠናከረው የሽብርተኝነት ስጋት እና የፀጥታ ጥበቃ ርምጃ ሮም የሚገኘውን ወኪላችን ተኽለእግዚ ገብረየሱስን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።
ተኽለእግዚ ገብረየሱስ
አርያም ተክሌ
ሸዋዬ ለገሠ