1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

'የሻገተ ዜና' እና ሮቤል ተመስገን

ዓርብ፣ ጳጉሜን 4 2008

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አለ የሥነ-ጥበብ ትምህርት ቤት መምህር የሆነው ወጣት ሮቤል ተመስገን በኢትዮጵያ የጋዜጠኞች እና ጸኃፍትን የህይወት ውጣ ውረድ 'የሻገተ ዜና' የተሰኘ ሥራ በመስራት ላይ ይገኛል።

https://p.dw.com/p/1JzRD
Robel Temesgen Another Old News Projekt
ምስል Institut fur Raumexperimente 2014

'የሻገተ ዜና' እና ሮቤል ተመስገን

ከዚህ ቀደም በለንደን አድባር የተሰኘ ሥራውን ለእይታ ያቀረበው ሮቤል በኢትዮጵያ መንግስት ክስ ተመስርቶባቸው የተዘጉ ጋዜጦች ላይ ትኩረት አድርጓል። ሮቤል ተመስገን በርሊን ከተማ በሚገኘው አካዳሚያ ዴር ኩንስተ የጥበብ ማዕከል 'የሻገተ ዜና' የሚል ርዕስ የሰጠውን የጥበብ ስራ በመሥራት ላይ ይኛል። ሮቤል በማዕከሉ የሚቆየው ለሶስት ወራት ብቻ ሲሆን በሥራው ሰዓሊው ከዚህ ቀደም ከለመደው አሰራር ወጣ በማለት ራሱን ለመፈተሽ የጀመረው ነው።ሮቤል ባለፉት ዓመታት የታዘበውን የጋዜጠኞች፤ እና ጸሃፍት እስር እና እንግልት በተለየ አተያይ ለማቅረብ ደፋ ቀና እያለ ነው።
Robel Temesgen Künstler Äthiopien
ምስል Humle Isabella Rosenkvist
ደሴ ተወልዶ ያደገው ሮቤል ተመስገን መጀመሪያ ከስዕል ጋር የተዋወቀው በወንድሙ የሥዕል ስቱዲዮ ወንድሙ እን የወንድሙ ጓደኞች በሚሰሯቸው ሥዕሎች ነበር። በወንድሙ የሥዕል ስቱዲዮ እጁን ያፍታታው ወጣት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲው አለ የሥነ-ጥበብ ትምህርት ቤት ተምሯል። ወጣቱ እንደ ሥነ-ጥበብ ባለሙያ እና ኃፊነት እንደሚሰማው ሰው ይህን ሥራ ለመስራት መነሳቱን ይናገራል።
እሸቴ በቀለ
ነጋሽ መሐመድ