የሻማ ማብራት ሥነ-ሥርዓት ለብርቱካን ሚዴቅሳ
ሐሙስ፣ ጥር 21 2001ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ መንግሥት ያሠራቸዉን የአንድነት ለፍትሕና ለዲሞክራሲ ፓርቲ መሪ ወይዘሪት ብርቱካን እንዲለቅ አዲስ አበባ የሚኖሩ የፓርቲዉ አባላትና ደጋፊዎች ጠየቁ።ትናንት ከፓርቲዉ ፅሕፈት ቤት ቅጥር ግቢ የተሰበሰቡት የፓርቲዉ አባላትና ደጋፊዎች ወይዘሪት ብርቱካን የታሰሩበትን አንደኛ ወር ሻማና ጧፍ በማብራት አስበዉታል።የፓርቲዉ ባለሥልጣናት እንደሚሉት ወይዘሪት ብርቱካንን ለማስለቀቅ ፖለቲካዊ፥ ሕጋዊና ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴዎቻቸዉን አንደቀጠሉ ነዉ።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ ዝር ዝር ዘገባ ልኮልናል።