የሶማሊያ የባሕር ላይ ወንበዴዎችና ማስጠነቀቂያዉ
ማክሰኞ፣ ነሐሴ 29 2004ማስታወቂያ
የሶማሊያን የባሕር ወንበዴዎች ጥቃት ለመከላከል የመርከብ ኩባንዮች የዘረጉትን የጥበቃ መርሐ-ግብር አጠናክረዉ እንዲቀጥሉ ወንበዴዎቹን ለመዉጋት የዘመተዉ ጦር አሳሰበ።የሶማሊያ የባሕር ላይ ወንበዴዎች መርከቦችንና ባሕረኞችን ማገት ማጥቃታቸዉ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ መጥታቱ እየተነገረ ነዉ።ወንበዴዎቹን ለመዉጋት የዘመተዉ የአታላንታ፥ የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅትና (ኔቶ) የሌሎችም ጦር ዕዝ አዛዦች ትናንት በጋራ እንዳስታወቁት ግን ወንበዴዎቹ ዳግም አንሰራርተዉ ጥቃት ሊያደርሱ ይችላሉ።በዚሕም ምክንያት የመርከብ ኩባንዮች መርከቦቻቸዉንና ሠራተኞቻቸዉን ከማስጠበቅ መቦዘን የለባቸዉም።የብራስልሱ ወኪላችን ገበያዉ ንጉሴ ዝር ዝር ዘገባ አለዉ።
ገበያዉ ንጉሴ
ነጋሽ መሃመድ
ተክሌ የኋላ