የስፖርት እና የባህል ትዕይንት በኑረንበርግ
ሐሙስ፣ ሐምሌ 28 2003ማስታወቂያ
በእዚህ ለሶስት ቀናት በዘለቀዉ ትዕይንት ላይ በተለያዩ አዉሮጳ አገሮች የሚኖሩ ኢትዮጽያዉያን የሚገኙበት ሃያ ሶስት የእግር ኳስ ቡድኖች ዉድድር አድርገዉ የዘንድሮዉን ግጥምያ ኢትዮ-ሆላንድ ኢትዮጽያዉያኑ የእግር ኳስ ቡድን ማሸኘፉ ተገልጾአል። በዝግጅቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት በአሁኑ ወቅት በስዊትዘርላንድ ነዋሪ የሆኑት አትሌት መሃመድ ከዲር ነበሩ። ዘንድሮዉ ለዘጠነኛ ግዜ በኑረንበርግ የተካሄደዉ የኢትዮጽያዉያን መድረክ ከምንግዜዉም በላይ የተሳካለት እንደነበር፣ በቦታዉ የተገኙ እደምተኞች ገልጸዉልናል። በሌላ በኩል በኑረንበርግ ይህ የኢትዮጵያ የባህል እና የስፖርት ትዕይንት የተካሄደበት ቦታ በጀርመን በቱሪዝሙ ዘርፍ ተወዳጅ እና በርካታ የአለም አገራት ህዝብ የሚጎበኘዉ ቦታ መሆኑም ታዉቋል። ስለ ኑረንበርጉ የሶስት ቀናት የኢትዮጵያዉያን የስፖርት እና የባህል መድረክ መሰናዶ ይዘናል ያድምጡ!
አዜብ ታደሰ
አርያም ተክሌ