የስኳር ልማት ፕሮጀክትና ዋልድባ
ሐሙስ፣ መጋቢት 13 2004ማስታወቂያ
ዋልድባ ገዳም አቅራቢያ የሚከናወነዉ የስኳር ፋብሪካ ግብታና የሸንኮራ አገዳ ተክል ልማት የገዳሙን ይዞታ ይነካል የሚለዉን ዘገባ የኢትዮጵያ የስኳር ኮርፖሬሽን አስተባበለ። ፕሮጀክቱ በምዕራባዊ ትግራይ ዞን በወልቃይት ወረዳ እንደሚከናወን ያመለከቱት የኮርፖሬሽኑ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ በሂደቱም ሶስት አብያተ ክርስቲያናት ሊነሱ እንደሚችሉ ለዶቼ ቬለ ገልፀዋል። በአንፃሩ በሂደቱ እንደሚፈርሱ የተገለፀዉ አብያተ ክርስቲያናት የገዳሙ ይዞታ ሆኖ ከሚታወቀዉ ስፍራ ላይ የሚገኙ እንደሆኑ የገዳሙ መነኮሳት ይናገራሉ።
ሸዋዬ ለገሠ
ሂሩት መለሠ