የስኮትላንድ የህዝበ ውሳኔ ጥያቄ
ዓርብ፣ መጋቢት 22 2009ማስታወቂያ
ብሪታንያ ከአውሮጳ ኅብረት አባልነት መልቀቂያ ይፋ ማመልከቻ ካስገባች ከሁለት ቀናት በኋላ ስተርጀን በጻፉት ደብዳቤ የስኮትላንድ ህዝብ መፃኤ ዕድሉን የመወሰን መብት አለው ብለዋል። ባለፈው ሰኔ በተካሄደው የብሪታንያ ከአውሮጳ ኅብረት መውጣት አለመውጣት ህዝበ ውሳኔ ላይ ሶኮትላንዶች ከኅብረቱ ጋር መቆየትን ነበር የመረጡት። በጎርጎሮሳዊው 2014 ስኮትላንድ ከብሪታንያ ትነጠል አትነጠል በሚለው ጥያቄ ላይ በተካሄደው ህዝበ ውሳኔ ከህዝቡ 55 በመቶው ከብሪታንያ ጋር መቆየትን መርጦ ነበር። ሆኖም ስተርጀን ከዚያን ወዲህ ሁኔታዎች በመለዋወጣቸው ሌላ ህዝበ ውሳኔ ማካሄድ ያስፈልጋል ነው የሚሉት። ስተርጀን ስኮትላንድ ከኅብረቱ ጋር እንድትቆይ ቢጠይቁም የብሪታንያ መንግሥት ተቃውሞታል። የስኮትላንድ ፓርላማ ሁለተኛ ህዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ ባለፈው ማክሰኞ በ69 በመቶ አብላጫ ድምጽ ተስማምቷል። ሆኖም ካለለንደን መንግሥት ይሁንታ ህዝበ ውሳኔው ሊካሄድ አይችልም።
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ