የሲና ድንበርና ተደጋጋሚ ጥቃት
ረቡዕ፣ ነሐሴ 9 2004ማስታወቂያ
ባለፈው ዓመት፣ እስራኤልን ፍልስጤምንና ግብጽን በሚያዋስነው የሲና ድንበር ከተማ በባንክና በፖሊስ ጣቢያዎች ባካሄዱት ጥቃት ሰባት ሰወችን ገደሉ የተባሉ 14 የአንድ ጽንፈኛ ቡድን አባላት በሞት እንዲቀጡ በስዊዝ የእስማኤልያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ትናንት ውሳኔ ማሳለፉ ግብጽ ውስጥ የሚሰራጩ የመገናኛ ብዚሃን ዘገባ ያስረዳል፡፡ ሙት በቃ የተበየነባቸው፣ 14ቱ የተዋህድ ወአል ጀሃድ ተብሎ የሚጠራው የጽንፈኛ ቡድን አባላት ምርመራ ከአመት በላይ እንደወሰደና ተጠርጣሪዎች በሽብር ጥቃቱ ቀጥተኛ ተሳታፊዎች ለመሆናችው ተጨባጭ መረጃዎች ቀርበው የሞት ፍርድ ቅጣት እንደተላለፈባቸው በዝርዝር አስታውቋል፡፡
ባለፈው ሳምንትም ሲና ውስጥ ፣ ራፋህ ኬላ ፤ 16 የሚሆኑ ግብጻውያን ድንበር ጠባቂዎች፣ በጽንፈኞች ደረሰ በተባለው ድንገተኛ ጥቃት መገደላቸው መነገሩ የሚታወስ ነው። ያን የመሰለ ጥቃት እንዴት ሊሰነዘር ቻለ? በሲና በተደጋጋሚ ስለደረሰው ጥቃትና ስለግብፅ መንግሥት አጸፋዊ እርምጃ ነቢዩ ሲራክ
ነቢዩ ሲራክ
ተክሌ የኋላ
ሸዋዬ ለገሠ