የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት በድርድር እንዲቋጭ የሚደረገው ግፊት
ረቡዕ፣ ጳጉሜን 3 2013ማስታወቂያ
በሰሜን ኢትዮጵያ በቀጠለው ጦርነት ተፋላሚ ወገኖች ተኩስ አቁመው ልዩነታቸውን በጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት እንዲፈቱት ዓለም አቀፍ ግፊት እየተደረገባቸው ይገኛል። በጉዳዩ ላይ ዶይቸ ቨለ ያነጋገራቸው ደህንነትና ፍትሕ ለትግራይ የተባለው ድርጅት ምክትል ኘሬዚዳንት ኘሮፌሰር ሙሉጌታ ገብረ እግዚአብሄር ነፃ የሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማት ድርድሩን ማካሄድ አለባቸው ባይ ናቸው። በዳይተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ መምህር ዶክተር መሣይ ከበደ በበኩላቸው ጦርነቱ በድርድር መቆም ቢገባውም ህወሓት ለዚህ የሚመች ድርጅት አይደለም ይላሉ። እንደ ዶክተር መሣይ ኢትዮጵያ በጦርነቱ የበላይነት አግኝታ በትግራይ ለሠላም ዝግጁነት ያለው ሌላ ተለዋጭ ፖርቲ ለድርድር መውጣት ይኖርበታል።
ታሪኩ ኃይሉ
ሸዋዬ ለገሠ
ነጋሽ መሐመድ