የማማ አፍሪቃ 75ኛ አመት ክብረ በአል
ሐሙስ፣ መጋቢት 13 1999ማስታወቂያ
ፓታ ፓታ በተሰኘዉ ሙዚቃዋ በጣም በሚስደንቅ ሁኔታ በአለም ዙርያ በአንድ ግዜ ተደናቂነትን ማትረፉ አስገራሚ ነበር። ትዉልዷን እ.አ የካቲት 25 / 1932 በደቡብ አፍሪቃ ጆሃንስበርግ አካባቢ ባለች መንደር እንደሆነ የምትናገረዋ ማርያ ማኪየቫ ፈጣሪዮ በሰጠኝ ስጦታ ትላለች፣ አንድ ግዜ በሰጠችዉ ቃለ ምልልስ ከፈጣሪዩ የተሰጠኝ ተስፈኛነት ቆራጠኝነት እና ማዜም ናቸዉ። በተስፍ እና በቁርጠኝነት በምትቃኛቸዉ ዜማዎችዋ በደቡብ አፍሪቃ አፓርታይድን በመቃወም እንቅስቃሴዋን ዳር አድርሳለች። ማርያ ማኬቫ በተስፍ በቁርጠኝነት በማዜም በጀመረችዉ ፓለቲካዊ እንቅስቃሴዋ የአፍሪቃዉያን በተለይ የአገሯን ሴት ሙዚቀኞች ወደ መድረክ እንዲወጡ ምሳሌ ሆናለች። በአገራችን በአዲስ አበባ የአሁኑ አፍሪቃ ህብረት የቀድሞዉ የአፍሪቃ ህብረት ድርጅት ጉባኤ ላይ ተገኝታ ፁሁፋን አቅርባለች በተለይ በአራችን ከነበሩት ከታዋቂዎቹ ከያኔዎች መካከል ከሜሪ አርምዴ ጋር ተገናኝታ እንደነበር ይነገራል። የአገራችን የሙዚቃ ንጉስ የጥላሁን ገሰሰን የጥንቱ ትዝ አለኝ የተባለዉን ዜማ በማቀንቀኗ ታዋቂነትን አትርፋለች።