የመጀመሪያዎቹ የአፍሪቃ ኅብረት ሰላም አስከባሪ ሠራዊት በሶማልያ28 የካቲት 1999ረቡዕ፣ የካቲት 28 1999የሞቃዲሾ ጊዚያዊ ሁኔታ፥ ተቀናቃኞቹ ጎሣዎች፥ እንዲሁም፡ የዩጋንዳ ሰላም አስከባሪ ወታደሮች በሶማልያ መሠማራት፡ የመቃዲሾን ሁኔታና ሰላም በተመለከተ አርያም ተክሌ የሸበሌን ጋዜጠኛ አዌስ ዩሱፍ ኦስማንን በስልክ አነጋግራለች።https://p.dw.com/p/E0Ygየሶማልያ ሚሊሺያዎችምስል APማስታወቂያየሶማልያ ጎሣዎችና የሽግግሩ መንግሥት ውዝግብ ሶማልያ ውሽጥ ከፍተኛ አባላት ያሉት የሀዊያ ጎሣ መሪዎች የሽግግሩ መንግሥት የሚከተለውን አሠራርና መርሕ ተቃወሙት። የሽግግሩ መንግሥት ባለሥልጣናት ግን የጎሣ መሪዎቹን ተቃውሞ ነቅፈውታል። የሶማልያን ሰላም ለማስከበር ከሚዘምተው ያፍሪቃ ኅብረት ሠራዊት ደግሞ የመጀመሪያው የሆነው የዩጋንዳ ጓድ መቃዲሾ እየገባ ነው።