የመድረክ ወቀሳና የመንግሥት ማስተባበያ
ሐሙስ፣ ግንቦት 26 2002ማስታወቂያ
ሥምንት ፓርቲዎችን የሚያስተናብረዉ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ በሺ የሚቆጠሩ አባላትና ደጋፊዎቹን መንግሥት አሰራቸዉ በማለት ወቀሰ።የመድረክ ከፍተኛ ባለሥልጣን ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና እንዳስታወቁት በተለያዩ ቦታ የሚገኙ የፓርቲዉ አባላትና ደጋሪዎች እየታሰሩ ነዉ።የኢትዮጵያ መንግሥት ቃል አቀባይ አቶ ሽመልስ ከማል ግን ከምርጫዉ በሕዋላ የታሰረ የተቃዋሚ አባል የለም ብለዋል።የኢትዮጵያን ፖለቲከኞች ለማስታረቅ የሐገር ሽማግሌዎች ጣልቃ ገብተዋል መባሉን፥ ፕሮፌሰር መረራ «ሞክረዉ» ነበር ሲሉ፥ አቶ ሽመልስ ሽምግልና የሚያስፈልገዉ ነገር የለም ብለዋል።መሳይ መኮንን ሁለቱን ባለሥልጣናት አነጋግራቸዋል።
መሳይ መኮንን
ተክሌ የኋላ