የመኪና አስመጪዎች ቅሬታ
ማክሰኞ፣ ግንቦት 26 2006ማስታወቂያ
መኪናቸውን በኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክ አገልግሎት ድርጅት በኩል ከጅቡቲ ወደ ደረቅ ወደብ በሚያስገቡት ሰዓት እንደ ወንበር እና ጎማ የመሳሰሉ ነገሮች እየተሰረቁባቸው እና ለከፍተኛ ወጪ እንደተዳረጉ ይናገራሉ። የመኪና አስጫኞቹን ወቀሳ እና የድርጅቱን ምላሽ አግኝተናል።
ያነጋገርናቸው ከአውሮፓ መኪና ወደ ኢትዮጵያ የሚያስገቡ ነጋዴ እና ያስመጪ ንግድ ፍቃድ ስለሌላቸው፤ ፍቃድ ካለው ጓደኛቸው ጋር ተዋውለው መኪና ያስገቡ ግለሰብን ነው። ለግለሰቦቹ ቅሬታዎች በኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክ አገልግሎት ድርጅት የኢንሹራንስ እና የካሳ ክፍል ዳሬክተር የሆኑት አቶ ያሬድ ሽፈራው ለወቀሳዎቹ የሰጡት ምላሽ አለ።
ሁሉንም ከድምፅ ዘገባው ያገኙታል።
ልደት አበበ
ነጋሽ መሀመድ