የለገጣፎ ተፈናቃዮች እሮሮ
ረቡዕ፣ ግንቦት 28 2011ማስታወቂያ
በርከት ያሉ ሰዎች ተጠልለው ከሚኖሩበት ቤተ ክርስቲያን ተነስተው ቢመጡም ተስፋ የሌለው ምላሽ እንደጠበቃቸው በተለይ እናቶች በምሬት መድረሻ አጣን በማለት ነው የሚገልፁት። ያልሄድንበት ቅሬታ ያሰማንበት ቦታ እና ባለስልጣን የለም የሚሉት እነዚህ ሰዎች ሀገሪቱ ተፈናቃዮችን እየመለሰች ነው እየተባለ እኛን ግን እስካሁን ድረስ ያየን ባለስልጣንና የመንግሥት አካል አለመኖሩ ተስፋ አስቆርጦናል ብለዋል። በምሬት ሲያለቅሱ የነበሩ እናቶች ህይወት እንደከበዳቸውና ምንም የሚታያቸው ተስፋ እንደሌለ መንግሥት ግን እንዲደርስላቸውና ከክረምቱ ዝናብ እንዲከላከላቸው ፣ በዘላቂነትም የነበራቸውን ህይወት እንዲመሩ እንዲያግዛቸው ተማጽነዋል። በስፍራው ተገኝቶ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ሰሎሞን ሙጬ ተከታዩን ልኮልናል።
ሰሎሞን ሙጬ
ሸዋዬ ለገሠ
ማንተጋፍቶት ስለሺ