የተሽከርካሪዎች ዘረፋ
ረቡዕ፣ ሰኔ 5 2011ማስታወቂያ
ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ወደ ምሥራቅ ኢትዮጵያና በተቃራኒዉ የሚጓዙ መንገደኞችና አሽከርካሪዎች የሚፈፀምባቸዉ ዘረፋና ድብደባ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየባሰ መምጣቱን አስታወቁ። መንገደኞች፣ አሽከርካሪዎችና ረዳቶቻቸዉ እንደሚሉት በተለይ ምሥራቅ ሐረርጌ የሚገኙ አነስተኛ ከተሞችን ገንዘብ ሳይከፍሉ አቋርጦ ማለፍ አይቻልም። አቤት ባዮቹ እንደሚሉት በየከሞቹ መኪኖችን እያስቆሙ መንገደኞችና አሽከርካሪዎችን ወይም ረዳቶቻቸዉን እያስፈራሩ አንዳዴም እየደበደቡ ገንዘብ የሚቀበሉ ወጣቶች «ሃይ ባይ» አላገኙም። የምሥራቅ ሐረርጌ ፖሊስ ግን ዘራፊዎችን እየተቆጣጠርን ነዉ ባይ ነዉ።
መሳይ ተክሉ
ነጋሽ መሐመድ
አዜብ ታደሰ